Ethiopian Folktales

The Wicked Stepmotherየተረገመች የእንጀራ እናት

Gurage Zoneጉራጌ ዞን · 1 min readደቂቃ ንባብ

Text size Share

Narrated by Tessema Gebre

At the start of the story, the narrator says:
Wemaka notka.
(Let me tell you a story.)

The listeners reply:
Egi nismahe.
(OK, let me listen)

A woman had eight sons and a stepson called Kore. Kore was very brave and he brought captives from the battlefield. The eight brothers were jealous of him, because of his bravery. They wanted him to be killed and he was all alone without any supporter. The eight sons told their mother that they didn’t like the fact that they were not as brave as he was.

"Why can’t we get rid of him?” they said to her.

“All right,” she says. “I’ll send him to the forest so he will be eaten by an elephant.”

“Can you do that?”

“Yes, I can,” she says.

The mother says to Kore, “I am sick, my child. I want you to bring me medicine.”

“What kind of medicine?”

“The tail of an elephant.”

Kore was so brave that he killed an elephant and brought her the tail. The mother and her eight sons were disappointed that he was not eaten by the elephant so they looked for other ways to get rid of him.

“Now I’ll send him to the river to fetch water and you’ll ambush him there and drown him,” she said to them.

Again, she said to Kore, “I’m sick. I need water right now.”

And it was dark. He went to the river to fetch water and the brothers came with spears to kill him.

He escaped and he killed them one by one.

የተረገመች የእንጀራ እናት

በተሰማ ገብሬ የተተረከ

በተረቱ መጀመሪያ ላይ ተራኪው እንዲህ ይላል፤
ወማካ ኖትካ
(ተረት ልንገራችሁ)

አድማጩም እንዲህ ብሎ ይመልሳል፤
ኤጊ ኒስማሄ
(እሺ ላዳምጥህ/ሽ)

አንዲት ስምንት ወንድ ልጆችና አንድ ኮሬ የተባለ የእንጀራ ልጅ የነበሯት ሴት ነበረች፡፡ ኮሬ በጣም ጀግና ስለነበር ከጦር ሜዳ ምርኮኞች ይዞ ይመጣ ነበር፡፡ በዚህ ጀግንነቱ ስምንቱ ወንድማማቾች ይቀኑበት ነበር፡፡ እንዲገደልም ይፈልጉ ነበር፡፡ እርሱ ግን ማንም ረዳት የለውም ነበር፡፡ ስምንቱም ወንድማማቾች እንደርሱ ጀግና አለመሆናቸው እንደማያስደስታቸው ለእናታቸው ነገሯት፡፡

ወዲያውም “ለምን አናስወግደውም?” ብለው ጠየቋት፡፡

እርሷም “መልካም! እንግዲያው ወደጫካ ልኬው በዝሆን እንዲበላ አደርጋለሁ፡፡” አለቻቸው፡፡

“ይህንን ማድረግ ትችያለሽ?” ሲሏት

“አዎን እችላለሁ፡፡” አለቻቸው፡፡

ከዚህ በኋላ እናትየው ኮሬን “ልጄ ሆይ! ስለታመምኩ መድኃኒት እንድታመጣልኝ እፈልጋለሁ፡፡” አለችው፡፡

እርሱም “ምን ዓይነት መድኃኒት?” ብሎ ጠየቃት፡፡

“የዝሆን ጭራ!” ብላ መለሰች፡፡

ኮሬም በጣም ጀግና ስለነበረ ዝሆን ገድሎ ጭራውን ይዞላት መጣ፡፡ በዚህ ጊዜ እናትየውና ስምንቱ ወንድ ልጆቿ በኮሬ አለመበላት በጣም ተበሳጭተው ሊያስወግዱት ሌላ ዘዴ መዘየድ ጀመሩ፡፡

እናትየውም “አሁን ደግሞ እኔ ከወንዝ ውሃ ይዞልኝ እንዲመጣ ስልከው እናንተ አድፍጣችሁ ውሃ ውስጥ ወርውራችሁት ይሙት፡፡” አለቻቸው፡፡

ከዚያም ኮሬን “አሞኛልና በአስቸኳይ ውሃ ያስፈልገኛል፡፡” አለችው፡፡

ቀኑ መሽቶ ነበር፡፡ እርሱም ውሃውን ሊያመጣ ሲሄድ ወንድማማቾቹ ሊገድሉት ጦር ይዘው መጡበት፡፡ እርሱም ከጥቃታቸው አምልጦ አንድ በአንድ ገደላቸው፡፡

In the original voice — hear tales from Gurage Zoneጉራጌ ዞን, told in Gurage. Listen ›